Skip to main content

የቀቤና ልዩ ወረዳ

                          ህላዊ መስህብ

የቀቤና  ብሄረሰብ     የባህል  ማዕከል

ይህ  ግዙፍ  ባህል ማዕከል የሚገኘው በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በቀቤና ልዩ  ወረዳ ወልቂጤ    ከተማ ሲሆን ከአዲስአበባ  በ  150 ኪ.ሜ ርቀት ላይ  ይገኛል። ማዕከሉ ግንቦት      27/2015  ዓም ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።ባህል ማእከሉ በውስጡ ከ 1000 ሰው በላይ በአንድ ጊዜ ማስተናገድ የሚችል ደረጃውን የጠበቀ የስብሰባ አዳራሽ፣ለኪነጥበብ ዝግጅት እና ለአነስተኛ ስስብሰባዎች የሚያገለግሉ ሁለት መጠነኛ አዳራሾች፣የቀቤና ብሄረሰብ የባህል ሙዝየም፣መስጂድ ፣የቀቤንኛ ቋንቋ ማበልፀግያ ማዕከል፣የእንግዳ ማረፊያዎች እና ለልዩ ልዩ አገልግሎት የሚውሉ ቢሮዎችን ያካተተ የክልላችንን ገፅታ የሚያጎላ ግዙፍ የባህል ማዕከል ነው።
በመሆኑም ማዕከሉ    በአዲስ አአበባ እና በሆሳና    አማካይ ቦታ ላይ ለጉብኝት ምቹ በሆነ  ስፍራ ላይ   የሚገኝ  በመሆኑ ይምጡ እና   ይጎብኙ  ስለ   ቀቤና እና ስለ  ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ባህል እና         ታሪክ         ላይ        ሰፊ አስተማሪ እና አዝናኝ መረጃ ያገኙበታል።