Skip to main content

የቢሮው ተግባርና ሀላፊነት

  • የክልሉ ብሔረሰቦች ቋንቋ፣ ባህል፣ ቅርስና ኪነጥበብ እንዲጠበቁ፣ እንዲጠኑና እንዲታወቁ ያደርጋል፣

  • የክልሉ ብሔረሰቦች ታሪካዊና ባህላዊ ቅርሶች፣ የፊልምና የትያትር ዘርፎች እንዲለሙና እንዲጠበቁ ያደርጋል፣

  • የቱሪዝም እንዱስትሪዎች እንዲስፋፉ በዘርፉ ለሚሰማሩ ባለሀብቶች፣ ድርጅቶችና ማህበራት የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ ይሰጣል፣ ይቆጣጠራል በሕግ መሰረት ይሰርዛል፣

  • ማህበራዊ ዕድገትን የሚያጓትቱ አመለካከቶችን እና ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ለመከላከል የሚያስችሉ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን ያከናውናል፣

  • በክልሉ የሚገኙ ቁሳዊና ቁሳዊ ያልሆኑ የባህል ቅርሶችን ያሰባስባል፣ ይመዘግባል፣ እንዲጠበቁ ያደርጋል፣

  • በክልሉ ተፈጥራአዊ የቱሪዝም መስህቦችና የዱር እንስሳት መገኛ ቦታዎችን ያጠናል፣ አዋጭነታቸውን አረጋግጦ እንዲከለሉና እንዲጠበቁ ያደርጋል፣ ይቆጣጠራል፣

  • የቱሪዝም አገልግሎት ሰጪ ድርጅቶች እንዲስፋፉና የአካባቢው ሕዝብ ከቱሪዝም ልማት ተጠቃሚ የሚሆንበትን ስልት ይቀይሳል፣ ተግባራዊም ያደርጋል፣

  • የክልሉን ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ባህል፣ ቋንቋ፣ ታሪክና ቅርስ የሚያሳይ ቤተ-መዘክርና ባህላዊ መንደሮች ያደራጃል፣ ያስተዳድራል፣

  • በክልሉ የሚተዳደሩ የዱር እንስሳት ጥበቃ ክልሎችና ሌሎች የቱሪስት መስህብ ስፍራዎች የሚገኙ ገቢዎችን ይሰበስባል፣

  • በክልሉ ለሚገኙ የቱሪስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ክልላዊ ደረጃ ይሰጣል፣

በሰው ሃይል ሥልጠናና በሙያ ምክር አገልግሎት አማካይነት የቱሪዝም ዘርፍን የማስፈፀም አቅም ይገነባል፣

  • ለቱሪዝም ገበያ አስፈላጊ ሆነው የሚገኙ የዱር እንስሳት እርባታ ጣቢያዎችን እና ፓርኮችን  ያቋቁማል፣ ያስተዳድራል፡፡

  • በክልሉ የሚገኙ ፓርኮችን እንዲጠበቁ ያደርጋል፤ ልማትና አስተዳደራዊ ስራዎቻቸውን ይከታተላል፣ ይደግፋል፣